Получи случайную криптовалюту за регистрацию!

Ethiopian University መረጃ

Логотип телеграм канала @university_ethiopia_mereja — Ethiopian University መረጃ E
Логотип телеграм канала @university_ethiopia_mereja — Ethiopian University መረጃ
Адрес канала: @university_ethiopia_mereja
Категории: Образование
Язык: Русский
Количество подписчиков: 20.30K
Описание канала:

https://www.youtube.com/channel/UCaIvJ_Bd_-FgQR6Q_kYNcuA?sub_confirmation=1
ይህ ቻናል የኢትዮጵያ ዪኒቨርስቲ መረጃዎችን የያዘ ነውና join አድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UCaIvJ_Bd_-FgQR6Q_kYNcuA?sub_confirmation=1
@University_Ethiopia_Mereja

Рейтинги и Отзывы

1.67

3 отзыва

Оценить канал university_ethiopia_mereja и оставить отзыв — могут только зарегестрированные пользователи. Все отзывы проходят модерацию.

5 звезд

0

4 звезд

0

3 звезд

1

2 звезд

0

1 звезд

2


Последние сообщения

2023-05-31 08:30:02 #Update

በ2015 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠው አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከሐምሌ 03 እስከ 13 /2015 ዓ.ም እንደሚከናወን ይታወቃል፡፡

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ህብረት ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ያደረገውን ወይይት ተከትሎ አገር አቀፍ የመውጫ ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ ላይ ማሻሻያ ተደርጓል፡፡ በዚህም፡-

➤ በሰኔ 2015 ዓ.ም ሞዴል የመውጫ ፈተና ይሰጣል።

➤ የመውጫ ፈተናው ከሐምሌ 03 እስከ 08/2015 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

➤ ውጤት ከሐምሌ 09 እስከ 10/2015 ዓ.ም በተቋማቱ ይገለጻል፡፡ (ተማሪዎች ከሐምሌ 08 ጀምሮ የፈተና ቁጥራቸውን በማስገባት ኦንላይን ማየት ይችላሉ።)

➤ የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ከሐምሌ 10 እስከ 17/2015 ዓ.ም ይከናወናል፡፡

ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ህብረት

https://www.youtube.com/channel/UCaIvJ_Bd_-FgQR6Q_kYNcuA?sub_confirmation=1
5.9K views05:30
Открыть/Комментировать
2023-05-27 08:20:10 ማስታወቂያ

የተባበሩት ኤምሬትስ የሰጠውን ስኮላርሽፕ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ ተማሪዎች

የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግስት በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል ለመስጠት በተፈቀደው መሰረት ቀደም ሲል ከ09/08/2015 እስከ 15/08/2015 ድረስ በበይነ መረብ ምዝገባ መከናወኑ ይታወቃል፡፡

ስለዚህ በምዝገባው መሰረት ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በመጡ ባለሙያዎች ከግንቦት 24 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለተወዳደሪዎች የቃለ መጠይቅና የጽሁፍ ፈተና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሚሰጥ ስለሆነ፡

1. Group 1A and Group 1B ግንቦት 23 ቀን 2015 ዓ.ም
2. Group 2A and Group 2B ግንቦት 26 ቀን 2015 ዓ.ም በዋናው ግቢ በምድባቸው መሰረት እንድትገኙ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየገለፀ ለፈተና የምትቀርቡ ተማሪዎች የተመደባችሁበትን ዝርዝር መረጃ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ የተያያዘ መሆኑንን እንገልፃለን፡፡

A Complete List of Applicant Students for UAE Scholarship 2023 https://moe.gov.et/storage/Books/List%20of%20Applicant%20Students%20For%20UAE%20Scholarship%202023.xlsx
መልካም እድል

https://www.youtube.com/channel/UCaIvJ_Bd_-FgQR6Q_kYNcuA?sub_confirmation=1
8.3K viewsedited  05:20
Открыть/Комментировать
2023-05-21 15:55:21
ከትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ

............................................................................

የትውልድ የእውቀት አባቶች ፣ የሀገር ተረካቢ ዜጎች መሃንዲሶች የሆኑ ትውልድ ለማፍራት ደፋ ቀና ሲሉ መንገድ ላይ የቀሩ መምህራን ህልፈተ ህይወታቸው ልብ ይሰብራል!

የመደ ወላቦ መምህራን እንደ ወጡ መቅረታቸው ሀዘኑ መራር ነው። ፈጣሪ ለነፍሳቸው ዘላለማዊ እረፍትን ይስጥልን !

በአደጋው ጉዳት ደርሶባቸው ህክምና ላይ ለሚገኙ መምህራንም ፈጣሪ ምህረቱን ይስጣቸው!

አደጋው መላውን ህዝብ በተለይም ቅርባቸው የሆነው የትምህርቱን ማህበረሰብ እጅግ ያስደነገጠና ልብ የሚሰበር ለሙያ የተከፈለ መስዋዕትነት ነው።

ተማሪዎችን በእውቀት አንጸው ለመመለስ የወጡ መምህራን ወደቤተሰባቸው መመለስ ሳይችሉ በወጡበት በመቅረታቸው እጅግ አዝኛለሁ።

ለቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና ጓደኞቻቸው በሙሉ እንዲሁም ለመደ ወላቦ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ መጽናናትን እመኛለሁ።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ!
የትምህርት ሚኒስትር!
2.0K viewsedited  12:55
Открыть/Комментировать
2023-05-19 13:58:28 This can Important for Remedial and Grade 12 students
ይህ ለ Remedial ተማሪዎች እና ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ጠቃሚ ሊሆን ይችላል።
Please Subscribe to Help Me!!!
All Subjects are Available In this Channel



3.9K viewsedited  10:58
Открыть/Комментировать
2023-05-18 13:40:33
፨ለሁሉም የመንግስት ዩንቨርስቲዎች
፨ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
፨ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች

ጉዳዩ፡ የአገር አቀፍ ፈተና ቀናትን ስለማሳወቅ

1) በ2014 የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፤ ተቋማት ፈተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ።


2) በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ 13 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ።


3) የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ።

በመጨረሻም ከ2016 ጀምሮ የትምህርት ካላንደሩን ሁሉም ተቋማት ፕሮግራሞቻቸውን በዚህ ማዕቀፍ ያስተካክሉ ዘንድ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሳስበዋል።


https://www.youtube.com/channel/UCaIvJ_Bd_-FgQR6Q_kYNcuA?sub_confirmation=1
1.7K viewsedited  10:40
Открыть/Комментировать
2023-05-17 22:18:05 ዛሬ ከትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ለክልል ትምህርት ቢሮዎች ከተላከ ደብዳቤ ያገኘነው መረጃ

1) በ2014 የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፤ ተቋማት ፈተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ።


2) በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ 13 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ።


3) የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ።


        ፨ለጥቆማ
      https://www.youtube.com/channel/UCaIvJ_Bd_-FgQR6Q_kYNcuA?sub_confirmation=1
3.7K views19:18
Открыть/Комментировать
2023-05-17 12:44:42 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መቼ ይሰጣል?

በርካታ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከፈተና ቀን ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ጥያቄዎችን እየላኩልን ይገኛሉ።

ፈተናው በመጪው ሐምሌ ይሰጣል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፤ እስከአሁን የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ትክክለኛና ቁርጥ ያለ ቀን ይፋ አልተደረገም።

የፈተናው ቀን ይፋ የሚደረገው በማዕከል በኩል ከትምህርት ሚኒስቴር / ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ሲሆን ይህም ለህዝብ በይፋ በመገናኛ ብዙኃን ይነገራል።

በመሆኑም የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ተማሪዎች ለፈተናው ጥቂት ጊዜ የቀረው መሆኑን በመገንዘብ ዝግጅት ማድረጋችሁን እንድትቀጥሉ እንላለልን።

በሌላ በኩል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የተፈታኞች የበይነ መረብ ምዝገባ /online Registration/ አፈጻጸም ግምግማ ባለፈው ሳምንት አካሂዷል፡፡

በተጨማሪም በተዘጋጀው የፈተና አስተዳደር መመሪያ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን የበይነ መረብ ምዝገባው ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ የተደረገበትና ስኬትማ መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ የፈተና አስተዳደር መመሪያ ለተሳታፊዎች ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ከውይይቱ የተገኙ ሀሳቦችም በሰነዱ ተካተው በድጋሚ ለውይይት እንደሚቀርብና ሲጸድቅ ተግባራዊ እንደሚሆን ተነግሯል።

ጥያቄ ና አስተያየት ለመስጠት
 https://www.youtube.com/channel/UCaIvJ_Bd_-FgQR6Q_kYNcuA?sub_confirmation=1
3.9K views09:44
Открыть/Комментировать
2023-05-17 12:42:05 የድሬደዋ ዩንቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ከትምህርት ሚኒስቴር የተሠጡ አቅጣጫዎች በሚል ያጋራው መረጃ

1, የሬሜድያል ተማሪዎች ፈተና ሰኔ መጨረሻውዎቹ የሚሠጥ ይሆናል።

2, የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ሀምሌ የመጀመሪያዎቹ ሁለት ሳምንት ውስጥ የሚሠጥ ይሆናል።

3,  በ2ተኛ ወሰነ ትምህርት ያልተመዘገቡ እና ለምርቃት ብቁ ያልሆኑ የመጨረሻ ዓመት ተማሪዎች ቀጣይ አመት ፈተናው የሚወስዱ ይሆናል።(የዓመቱ መጀመሪያ ላይ)

4, የምርቃት ፕሮግራም በተመለከተ በተቋማት የሴኔት ውሳኔ ማድረግ የሚቻል ይሆናል።

5,  የፈተናው አጠቃላይ የጥያቄ መጠን እንደ ትምህርት አይነቱ  ከ 100-150 ነው።

6, ማለፊያ ነጥብ 50% እና ከዚያ በላይ ነው።

7, ፈተናው የሚሠጠው በ online  ነው።

8,  የፈተናው ይዘት ሙሉ ምርጫ ነው።


        ፨ለጥቆማ
 https://www.youtube.com/channel/UCaIvJ_Bd_-FgQR6Q_kYNcuA?sub_confirmation=1
3.8K views09:42
Открыть/Комментировать
2023-05-16 18:28:22 #REMEDIAL #UEE #EXIT

ለሁሉም ተማሪዎች ሼር አድርጉ ለ Remedial ተማሪዎች Maths እና Physics ሙሉ ቲቶሪያል ተዘጋጅቷል።

የሪሜድያል ፈተና ከሰኔ 25-30/2015 ድረስ ይሰጣል።

የ2015 የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ከሀምሌ 05-14/2015 ድረስ ይሰጣል።

የ2015 ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከሀምሌ 17-27/2015 ድረስ ይሰጣል።

ፈተናዎቹ በዩንቨርሲቲዎች በሚሰጡበት ጊዜ ተፈታኝ ያልሆናቹህ መደበኛ ተማሪዎች ከግቢ የምትወጡበት እና ወደ ግቢ የምትመለሱበትን ቀን ከዩንቨርሲቲዎቻቹህ updated academic calendar ላይ ተመልከቱ

ጥያቄ ና አስተያየት ለመስጠት
  https://www.youtube.com/channel/UCaIvJ_Bd_-FgQR6Q_kYNcuA?sub_confirmation=1
5.7K views15:28
Открыть/Комментировать
2023-04-29 14:31:47 #MoE #ExitExam

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በመጪው ሀምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች #በኦንላይን ለሚካሄደው የመውጫ ፈተና 30 ሺህ ኮምፒውተሮች ዝግጁ መሆናቸውን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ ፤ ከ240 ሺህ በላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል።

በዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የማያልፉ ተማሪዎች ድግሪ የማይሰጣቸው በመሆኑ ተማሪዎች ለሚሰጠው ፈተና ራሳቸውን አንዲያዘጋጁ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

በሀምሌ ወር ከሚሰጠው ፈተና በፊት በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ የሙከራ ፈተና እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ሚኒስቴሩ ፤ በኦንላይን ፈተናው መሰጠቱ ኩረጃን ለማስቀረት፣ የወረቀት ወጪና ማጓጓዣን ለመቀነስ ይረዳል ብሏል።

ለፈተናው በአጠቃላይ ከ15 በላይ ኮርሶች በየትምህርት መስኩ ተወጣጥተው ዝግጁ መሆናቸውን የገለፀው ሚኒስቴሩ " የፈተናው ውጤት በኦንላይን ይፋ የሚደረግና ሚስጥራዊነቱ የተጠበቀ ይሆናል " ብሏል።

ፈተናውን የማያልፉ ተማሪዎች ያለገደብ በተደጋጋሚ የመፈተን እድል እንደሚኖራቸው በመመሪያ መቀመጡን ያስታወሰው ትምህርት ሚኒስቴር " የመውጫ ፈተናው የተለየ ዓላማ የሌለው እና የተማሩትን ብቻ የሚመዝን በመሆኑ ተማሪዎች ሳይደናገጡ እንዲዘጋጁ ለተማሪዎች ጥሪ አቅርቧል።

ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመፈተኛ ጣቢያ እንደሚሆኑ ይፋ ተደርጓል።

#ኢብኮ
ጥያቄ ና አስተያየት ለመስጠት

https://www.youtube.com/channel/UCaIvJ_Bd_-FgQR6Q_kYNcuA?sub_confirmation=1
3.2K views11:31
Открыть/Комментировать